የኢንስቲትዩቱ ሴኔት የተለያዩ አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን አሳለፈ። *****ሰኔ11/ 2017 ዓ.ም*****
የኢንስቲትዩቱ ሴኔት የ2017 ዓ.ም የስልጠና ጊዜ በሚመረቁ ሰልጣኞች ጉዳይና በኢንስቲትዩቱ አካዳሚክ መምህራን የደረጃ ዕድገት ጉዳይ ተወያይቶ ወሳኔ ሰጥቷል።
ከኢንስቲትዩቱ ዋናው ግቢና የሳተላይት ካምፓሶች፣ በቅድመ-ምረቃና እና በድህረ-ምረቃ መርሀ- ግብር የሬጅስትራርና አልሙናይ ዳይሬክቶሬት ባቀረበው ሪፖርት መሰረት ስልጠናቸውን በስኬት ያጠናቀቁ ሰልጣኞች እንዲመረቁ ሰኔቱ ወስኗል።
በውሳኔው መሰረት ከ1ሺ ሀምሳ በላይ ሰልጣኞች በሁለቱ መርሃ-ግብሮች በስልጠና ዓመታት ማሟላት በሚጠብቅባቸውን ብቃት፣ ክህሎትና አመለካካት አሟልተው ተገኝተዋል።
ሰልጣኞቹ በቀን፣ በማታ እና በቅዳሜና እሁድ ፕሮግራሞች ስልጠናቸውን የተከታተሉ ሲሆን ሰኔ 15/2017 ዓ.ም በኢንስቲትዩቱ በሚዘጋጀው ደማቅ ስነስርዓት ይመረቃሉ።
በተያያዘም ሰኔቱ በኢንስቲትዩቱ አካዳሚክ መምህራን የደረጃ ዕድገት ረቂቅ መመሪያ ላይ የተወያየ ሲሆን፣ ተጨማሪ ግብዓቶችን አክሎ እንዲዳብር እና ለመጨረሻ ውሳኔ እንዲጠናቀቅ ለአርቃቂው ቡድን መርቷል።
Website: http://www.ftveti.edu.et/