ኢንስቲትዩቱ በዓመቱ የያዛቸው እቅዶች እንዲሳኩ የሪፎርም ቡድኖች ሚና የላቀ እንደሆነ ተገለጸ።
ኢንስቲትዩቱ በዓመቱ የያዛቸው እቅዶች እንዲሳኩ የሪፎርም ቡድኖች ሚና የላቀ እንደሆነ ተገለጸ።
***********መጋቢት 11/2017*******
የኢፌዲሪ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ብሩክ ከድር በኢንስቲትዩቱ ሥራ ላይ ያሉ የሪፎርም ቡድኖችን የቀጣይ ወራት የተግባር መመሪያ ሰጥተዋል።
ዶ/ር ብሩክ በኦረንቴሽን ላይ እንደገለጹት ኢንስቲትዩቱ በሪፎርም እሳቤ አቅዶ በመተግበር አመርቂ ውጤት ሲያስመዘግብ መቆየቱን ገልጸዋል።
ባለፉት 9 ወራት ብቻ እንኳን በርካታ ውጤቶችን መመዝገባቸውን ገልጸው በቀጣይ ወራት በላቀ አፈጻጸም በመፈጸም የተያዙትን የዓመተ ልህቀት 2 ግቦች ማሳካት ይገባል ብለዋል።
ለ 9 የሪፎርም ቡድኖች ኦረንቴሽን የተሰጠ ሲሆን በኢንስቲትዩቱ እንደመሪ ተቋም ለአገራችን የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ሞዴል ለመሆን መስራት እንደሚገባ ተገልጿል።
ዩቲዩብ http://www.youtube.com/fdretvtinstitute
ዌብሳይት http://www.ftveti.edu.et/
ፌስቡክ https://www.facebook.com/TVTI.EDU.ET
ቴሌግራም https://t.me/fdretvtinstitute
ቲክቶክ www.tiktok.com/@fdretvtistitute