ኢንስቲትዩቱ የአቅመደካማ ቤቶችን ሠርቶ ለማስረከብ ስራ ጀመረ። ***ጥቅምት 12/2017********

የኢፌዲሪ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ማህበረሰባዊ አገልግሎት መስጠት ከተሠጡት ተልዕኮዎች አንዱ ሲሆን ከሠሞኑ በየካ ክፍለከተማ ወረዳ 9 የሚገኙ የአቅመ ደካማ ቤቶችን ሰርቶ ለማስረከብ ስራ ጀምሯል።
የኢንስትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ብሩክ ከድር እና ማኔጅመንት አባላት ሥራው ያለበትን ሁኔታ በአካል ተገኝተው ክትትል አድርገዋል።
የኢንስቲትዩቱ የሁለተኛ ዲግሪ ሰልጣኞች ፕሮጀክቶቻቸውን ችግር ፈቺ ተግባራት ላይ እንዲውል በያዘው አቅጣጫ መሠረት እነዚህን የአቅመ ደካማ ቤቶች በሠልጣኞች እየተሰሩ እንደሚገኙ ተገልጿል።