ለቴክኒክና ሙያ ዘርፍ አመራሮች ሲሰጥ የነበረው የአቅም ግንባታ ስልጠና ተጠናቀቀ
የደቡብ ኮሪያ ዓለም አቀፍ ትብብር ኤጀንሲ (ኮይካ) ላለፉት አምስት ቀናት ለቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ከፍተኛ አመራሮች ሲሰጥ የነበረውን ስልጠና ዛሬ ተጠናቋል።
መንግስት የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ስልጠና ጥራት የሚያሻሽሉ የተለያዩ እርምጃዎች እየወሰደ መሆኑን የጠቆሙት ሚ/ር ዴኤታው መሰል ድጋፎች ፋይዳቸው የጎላ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
የኮሪያ ዓለም አቀፍ ትብብር ኤጀንሲ (ኮይካ) የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ጥራትን ለማሻሻል እያደረገ የሚገኘው የግብዓት እና የአቅም ግንባታ ድጋፍ የሚደነቅ መሆኑን በመገለጽ ለተደረገው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል።
ኮርያና ኢትዮጵያ በማኑፋክቸሪንግ፣ ግብርና፣ ቱሪዝም፣ ትምህርትና ሌሎች ዘርፎች ለይ በአጋርነት እየሰሩ መሆኑንም ተገልጿል።
ሐምሌ 19/2016 ዓ.ም
ለወቅታዊ ትኩስ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር