ተቋማዊ አቅሞችን በማቀናጀት ተኪ ቴክኖሎጂዎችን በስፋት ለማምረት ያለመ ትብብር ። **********ግንቦት 13*********
ዶ/ር ብሩክ ኢንስቲትዩቱ በሠመር ካምኘ እና በመደበኛ ፕሮግራም ቴክኖሎጂዎችን በስፋት እያተመረተ መሆኑን ገልፀው የሚመረቱ ቴክኖሎጂዎችን ለማስፋት እንደነዚህ አይነት ትስስሮችን ፈጥሮ እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል ።
ትስስሮቹ በዋናነት ሁለት ማዕቀፎች ላይ የሚያተኩር ሲሆን አንዱ የቢዝነስ ትስስር ሲሆን ይህም በተለይም ድርጅቶቹ ከኢንስቲትዩቱ የቴክኖቢዚያ ኢንተርፕራይዝ ጋር የሚተሳሰሩበትን ሁኔታ የሚይዝ ሲሆን ሌላኛው የትብብር ማዕቀፍ የክህሎት ልማት ስራዎች ላይ ሲሆን ኢንስቲትዩቱ በፍላጎት እና በጥናት ላይ የተመሠረቱ ስልጠናዎችን የሚሰጥበት እንደሚሆን ዋና ዳይሬክተሩ ገልፀዋል።